ማዕበል ተነስቶ – ግጥም
በኩባያ ውሃ ማዕበል ተነስቶ
ሁሉን ሲያናውጠው ውሽት ስሩን ሰዶ
እኛም ተሳፋሪ በጊዜአዊው ጀልባ
በዘር ተጠግተን እንጀራ ልንበላ።
አክ እንተፍ በለው አንተ ሰው ይቅርብህ
እልፍ እያለቀሰ አይበጅም መሳቅህ።
ጊዜ – ጊዜ የለው ያልፋል እንደ ጥላ
የመኖር ጉም ይዞህ መስሎህ የማይነጋ
ከበዙዎች ነጥቀህ ፎቆችን በትሰራ
አርቅህ በታኖር ንዋይ በጆኒያ
ጨለማው ሲረታ በብርሃን ሲተካ
የት ልትደበቅ ነው ብርሃኑ ሲመጣ?
(አደፍርስ ተሰማ – 2003 ዓ.ም)