ሊቢያ አሳዳሪ ያጣች ሐገር

የሕዝቧን መሠረታዊ ፍላጎት አሟልታ በማኖር ከአፍሪቃ አቻ ያልነበራት ሐገር ዛሬ የአሸባሪዎች፤የጎጠኞች፤ የሽፍቶች፤የስደተኛ አስተላላፊዎች፤ የዘራፊዎች መናኸሪያ ሆናለች።ከአራት ዓመት በፊት አንድ መሪ ነበራት።ዛሬ አስራ-ሰባት ሺሕ መሪዎች የሚያዙት አስራ-ሰባት ሺሕ ታጣቂ ቡድናት ይርመሰመሱባታል።