የስፖርት ዘገባ፤ የካቲት 9 ቀን፣ 2007 ዓ.ም.

ሊዮኔል ሜሲ ዳግም ሐትሪክ ሠርቷል፤ ቡድኑ ባርሴሎና ላቫንቴን 5 ለዜሮ በመርታት ከመሪው ሪያል ማድሪድ ጋር ትንቅንቁን አጠናቅሮታል። በቡንደስሊጋው ባየር ሙይንሽን ሐምቡርግን 8 ለባዶ አንኮታኩቷል። አርሰናል በእንግሊዝ FA Cup ድል ቀንቶታል። በጣሊያን ሴሪኣ ዝቅተኛ ነጥብ ያላቸው ኹለት ቡድኖች ኃያላኑን ቡድኖች ተፈታትነው ነጥብ አስጥለዋል።