የተራዘመው የናይጄሪያ ምርጫ እሰጥ አገባ

የካቲት 7 ቀን 2007 በናይጄሪያ ሊካሄድ የታቀደው ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ በስድስት ሳምንታት እንዲራዘም የሃገሪቱ ነጻ የምርጫ ኮሚሽን( Independent National Electoral Commission) ያሳለፈው ውሳኔ ከፍተኛ ትችት ገጥሞታል። የሃገሪቱ ጦር ሰራዊት በናይጄሪያ የዴሞክራሲ የስርዓት ግንባታ ጣልቃ እየገባ ነው የሚል ስጋት አይሏል።