የዘገየው ፀረ ኤቦላ ርዳታ

በኤቦላ ወረርሽኝ አስተላላፊ ተኀዋሲ የሚያዘው ሰው ቁጥር በርግጥ እየቀነሰ መጥቶዋል። ይህ ግን ችግሩ በምዕራብ አፍሪቃ ቀንሶዋል ማለት አይደለም። በመሆኑም፣ የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ በሽታውን በመታገሉ አኳያ ከዚሁ አካባቢ ጋር ትብብሩን ማጠናከር ይጠበቅበታል።