የአፍሪቃ መሪዎች ጉባኤና የክፍለ ዓለሙ ፀጥታ

የአፍሪቃ ህብረት አባል ሃገራት የመሪዎች ጉባኤ ክፍለ ዓለሙን በሚፈታተኑ ችግሮች ላይ ትኩረት ሰጥቶ እንደሚነጋገር ይጠበቃል ። ቦኮሃራም ፣ኤቦላ ማዕከላዊ አፍሪቃ ሪፐብሊክ እና ደቡብ ሱዳን ጉባኤው ከሚያተኩርባቸው ርዕሶች ውስጥ ይጠቀሳሉ ።ጉባኤው በአባል ሃገራት መዋጮ የሚሰማራ ፀረ ሽብር ኃይል ማቋቋም የሚቻልበትን መንገድም ይፈልጋል ።