“አቶ በላይ በዝረራ ነው የጣለኝን ፣ ጨብጬም ስሜዋለሁ” ትግስቱ አወል

“አቶ በላይ በዝረራ ነው የጣለኝን ፣ ጨብጬም ስሜዋለሁ” ትግስቱ አወል

ይህ በአቶ ትግስቱና በአንድ የአንድነት ደጋፊ መካከል ከተደረገ ልዉውጥ የተወሰደ ነው። በዚህ ልዉውጥ አቶ ትግስቱ ለፕሬዘዳንትነት ሲወዳደሩ ፣ በምክር ቤቱ አንድ ድምጽ ብቻ በማግነት (እርሱም የርሳቸው ብቻ ድምጽ) በተሸነፉበት ጊዜ ስለ አቶ በላይ ፍቃዱ የተናገሩት ይገኝበታል።

ደጋፊ

“ቃለ መሐላ ሲያደርጉ የሚይሳይ ፎቶ አየሁ። የአንድነት ሊቀመንበር ነኝ ብለው እየተናገሩ ነው። ስልጣን የሚወዱ ሰው እንደሆኑ ብዙዎች ይናገሩ ነበር። የምርጫ ቦርድ ያሰናከለዉን የመኢአድ እና አንድነት ዉህደት ቢሳካ ኖሮ፣ ዉህዱን ፓርቲ በፕሬዘዳንትነት ለመምራት ራስዎትን እጩ አደረጉ። ዉህደቱ እንደማይሆን ሲታወቅ ኢንጂነር ግዛቸው እንደገና ካቢኔያቸውን ሲያዋቅሩ የዉጭ ጉዳይ ሃላፊ ሆነው ተሾሙ። ለጊዜው የስልጣን ጥሞትን ትንሽ አረኩ። ዉች ካሉ ደጋፊዎችም ጋር መገናኘት ጀመሩ። ኢንጂነር ግዛቸው ከሃላፊነት ሲለቁ የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴያቸውን በተኑ። ለጥቂት ሳምንታት ያገኙት ስልጣን በማጣትዎት ተከፉ። በምክር ቤቱ በሕጉ መሰረት አዲስ ሊቀመነበር መመረጥ ስላለበት፣ ዴሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ እጩዎች ቀረቡ። እርስዎም እንደጋና እጩ ሆነው ቀረቡ። ከምክር ቤት አባላት አንድ ሰው ለርስዎ ድምጹን ሳይሰጠ ቀረ። አንድ ድምጽ ብቻ እርሱም እርስዎ ለራስዎት የሰጡትን ድምጽ ብቻ አገኙ። በአባላት ባለመመረጥዎት የተነሳ ራስዎትን መጠየቅ ሲገባዎት አኮረፉ። በዉስጥዎት በአንድነት ፓርቲ ላይ ቂም ቋጠሩ። አንድነት ደንቡን በማሻሻል የኮረም ቁጥር ማስገባት አለበት የሚል ሕገ ወጥ ጥያቄ ባቀረቡበት ጊዜ፣ አንድነት በትንሽ ነገር ግብግብ አያስፈልግም በሚል፣ ለአባላት ስልጠና ለመስጠት በማሰብ የጠቅላላ ጉባኤ ተጠራ። እርስዎም በጉባኤ ተገኝተው ፣ እርስዎ አንድ ድምጽ ሲያገኙ 26 ድምጽ፡ያገኙትን የአቶ በላይን አመራር ተቃዉመው ጠቅላላ ጉባዔው አመራሩን እንዲመርጥ ጠየቁ። ጠቅላላ ጉባኤ በርስዎ ፊት ምክር ቤቱ በደንቡ መሰረት ሊቀመነበሩን መምረጡን ትክክል እንደሆነ አረጋገጠ። በድጋሚም የአቶ በላይን ምርጫ አጸደቀ። እርስዎም አፈሩ። በዲሞክራሲና በሐሳብ ተሸነፉ።”የተማሩ ኖት። የማስተርስ ዲግሪ አልዎት። እንደ አዋቂ ቢያስቡና ቢያስተዉሉ ኖሮ ፣ ሌላ ጊዜ የአባላትን ድጋፍ በማግኘት ወደ ስልጣን ለመምጣት ይሰሩ ነበር። ሆኖም እልህ ተሞሉ። ህዝብን እያሸበረ ካለ ቡድን፣ ጋር ከሕወሃት ጋር አበሩ። “

አቶ ትግስቱ

ተወዳድረህ ሰው አልመረጠህም ያልከኝ፤ እውነት ነው፤ በዴሞክራሲያዊ ሂደት የሚጠበቅ ነው ። በመሆኑም እኮራለሁ እንጂ አላፍርበትም፡፡ በእለቱም በዝረራ የጣለኝን አቶ በላይ ፈቃዱን ጨብጬ ስሜዋለሁ ምርጫው ዴሞክራሲዊ እንደሆነ ገልጬ መልካም ምኞቴን ገልጫለሁ፡፡ በመቀጠልም በበላይ ክብኔ ስር ምክትል ሃላፊ ሆኜ እስከ ታህሳስ 3ቀን 2007 ጉባኤ እስከተደረገበት ድረስ አብሬ ነበር፡፡ እኔ ከፓርቲው ሳይሆን በሃሳብ ከነበላይ የተለየሁት በጉባኤው ወቅት ይህ ዛሬ በምርጫ ቦርድ የቀረበው ጥያቄ እንዳይመጣ በማሰብና ፓርቲዬን ለማዳን ያቀረብኩትን ደንባዊ አስተያዬት በእውቀት ሳይሆን በስሜት በ……… ጩኸት ተቀባይነት አላገኘም፡፡ በጩኸት የሚደረግ ውሳኔ ዴሞክራሲያዊ ተደርጎ በየዋሆች ሊወሰድ ስለሚችል፡፡ በድምፅ ተቃወምኩት፡፡ ከጉባኤው በኃላ በ ………… ፊታውራሪነት አንድነት የአባላቱ ሳይሆን በጣት የሚቆጠሩ ግለሰቦች አክሲዮን በሚመስል መልኩ አመራሩ እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ስገነዘብና በተለይ ……………. የፓርቲውን አባላት በንቀት ሲመለከትና የአመራሩ መታበይ ምክንያት የእነ አቶ አየለ ስሜነህን ውስጠ ፓርቲ ዴሞክራሲያዊ ትግል ተቀላቀልኩ፡፡”

እንግዲ እዚህ ላይ አቶ ትግስቱ ሐሳባቸውን ጠቅላላ ጉባኤው እንዳልተቀበለው አስቀምጠዋል። በአቶ በላይ በዝረራ እንደተሸነፉ ይናገራሉ። በዲሞክራሲ እንደሚያምኑም ጽፈዋል። አድንነትን ከምርጫ ቦርድ ከሚመጣ ችግር ለማዳን ስል፣ አቶ አየለ ስሜነህ የሚመሩትን ቡድን እንደተቀላቀሉ ይናገራሉ።

አቶ አየለ ስሜነህ በምርጫ ቦርድ የሚደረገው ደባ ስላልተመቻቸው በምርጫ ቦርድ በኩል በሕወሃት የሚደረገውን በሜዲያ በይፋ አጋልጠዋል። አቶ ትግስቱ ግን በምርጫ ቦርድ ገጸ በረከት የአንድነት ስርተፊኬት ለመቀበል፣ በምርጫ ያላገኙትን በምርጫ ቦርድ ስጦታ ለመቀበል እየተዘጋጁ ነው። አንድነትን ከምርጫ ቦርድ ለማዳን ሳይሆን የምርጫ ቦርድ መሳሪያና “ሰራተኛ” ሆነው አቶ ትእግስቱ ትልቅ ታሪካዊ ስሀተት እየሰሩ ነው።