የህወሓት ኣባል ኣልሆንም ያለ ኣስተማሪ በባለ ስልጣናት ከፍተኛ ድብደባ ደረሰበት

10933944_775340985890893_7985996265545061485_nፎቶው የምታዩት ሰውየ ገብረየሱስ ገብረሂወት የተባለ ኣስተማሪ ነው።

የምታዩት ፎቶ የህወሓት ኣባል ኣልሆንም ያለና በባለ ስልጣናት ከፍተኛ ድብደባ ደረሰበት ኣስተማሪ ነው።

መምህር ገብረየሱስ ገብረሂወት በደጉዓ ተምቤን ማሕበረስላሴ ትምህርት ቤት የሚያስተምር ነው።

የድብደባው መነሻ የህወሓት ኣባል ሆኖ መቀጠል ኣልፈልግም በማለቱ የመጣበት ጦስ ነው። ጦሱ ከደምወዙ በቀጥታ ለህወሓት ኣባልነት የሚል በየወሩ ሲቆረጥ ፍቃደኛ ባለ መሆኑና በተደጋጋሚ ሲቆረጥበት ወደ ፍርድ ቤት ሂዶ በመክሰስ ያለፍላጎቱ እንዳይቆረጥበት የሚል ፍርድ በመሰጠቱ የተበሳጩ የወረዳው ሃላፊዎች የወሰዱት ኣብዮታዊ እርምጃ ነው። ነፃ እርምጃ ማለት እንዲህ ኣይደለም..?
ህዝቡ ሳይወድ በግድ ኣባል ሁን ተብሎ የሚቆም መንግስት ምንያህል ዘለቄታ ይነሮዋል..? የደጉዓ ተምቤን የህወሓት ሃላፊዎች ግፋችሁ ለከት ብታበጁለት ይበጃቹሃል እንላለን። ገብረየሱስ ገብረሂወት ድብደባ ከደረሰበት በሗላ በከተማው ተጥሎ እስከ ለሊት ኣስር ሰዓት ተጥሎ ኣምሽተዋል።

ነፃነታችን በእጃችን ነው…!

10891506_775339539224371_393531670093231637_n
10686787_775340945890897_151639611470243883_n

The post የህወሓት ኣባል ኣልሆንም ያለ ኣስተማሪ በባለ ስልጣናት ከፍተኛ ድብደባ ደረሰበት appeared first on ሳተናው (Satenaw) – Latest & Current Ethiopian News, Breaking News,.