የኢትዮጵያን ቡና ማስተዋወቂያ ዝግጅት በፓሪስ

የኢትዮጵያን ቡና ወደ አዉሮጳ በብዛት በማስገባት ጀርመን ቀዳሚነቱን ይዛ ብትገኝም ፈረንሳይ ከዓመታዊ የቡና ፍጆታዋ ስድስት በመቶዉን የምታስገባዉ ከኢትዮጵያ መሆኑ ተሰምቷል። ሰሞኑን በፓሪስ ፈረንሳይ የኢትዮጵያን ቡና ፤ የኢትዮጵያን ባህልና የጥበብ ሥራዎችን የሚያስተዋዉቅ ዝግጅት በመካሄድ ላይ ይገኛል።