የሽብር ጥቃት ዛቻን ተከትሎ የ«ፔጊዳ» ሠልፍ ተሰረዘ
ከጀርመን ከተሞች፤ እንደ ድሬስድን እስልምና እንዳይስፋፋ የሚታገል ከተማ የለም። ባለፉት የሰኞ ሳምንታት ድሬስድን ውስጥ እስልምና እንዳይስፋፋ የሚታገሉ የፔጊዳ ደጋፊዎች ድሬስድን ከተማ ሰልፍ ሲወጡ ሰንብተዋል። የነገው ሰልፍ ግን የሽብር ጥቃት ሊሰነዘር ይችላል በሚል ፍራቻ ፖሊስ በከተማዋ ማንኛውም አይነት የአደባባይ ሠልፍ እንዳይደረግ አገደ።