‘የእነአየለ ስሜ አንድነት’ ፕ/ት ትዕግስቱ አወሉ:- “ብቸኛ አማራጭ ምጣዱን መስበር ነበር”

(ፋኑኤል ክንፉ) ታህሳስ 28 ቀን 2007 ዓ.ም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ባካሄደው አስቸኳይ ስብሳባ አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የፈጸማቸውን የሕግ ጥሰቶች በመመርመር እስከ ጥር 4 ቀን 2007 ዓ.ም ድረስ በሕጉና እና በፓርቲው መተዳደሪያ ደንብ መሰረት አሟልቶ እንዲያቀርብ በደብዳቤ ማሳወቁ ይታወቃል። ይህን የቦርዱ ጥያቄ ባይሟላ ቦርዱ የመጨረሻ ሕጋዊ እርምጃ በፓርቲው ላይ እንደሚወስድ በደብዳቤ ቁጥር አ/573/ፓ4/ጠ405 በተፃፈ ደብዳቤ መግለጽን ለማወቅ ተችሏል። የቦርዱን ማሳሰቢያ ከግምት በመውሰድ አንድነት ፓርቲ ጥር 1 ቀን 2007 ዓ.ም በፃፈው ደብዳቤ የሕግ እና የውስጥ ደንብ ሁኔታዎችን የመመርመር ሥልጣን ያለው ጠቅላላ ጉባኤ መሆኑን ጠቅሶ፣ አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤውን ጥር 3 ቀን 2007 ዓ.ም ቀበና መድሐኒዓለም አጠገብ በሚገኘው ጽ/ቤት ከጠዋቱ በ3፡00 ሰዓት ጀምሮ ለማድረግ መወሰኑን ለምርጫ ቦርድ በደብዳቤ አስታውቋል። በሌላ መልኩ ምርጫ ቦርድ ግልባጭ እያለ ለሚያሳውቃቸው “የእነአቶ አየለ ስሜነህ” የአመራር ቡድን በበኩላቸው፣ ታህሳስ 30 ቀን 2007 ዓ.ም በፃፉት ደብዳቤ ፓርቲው ጠቅላላ ጉባኤውን ጥር 3 ቀን 2007 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ጀምሮ በሳሬም ሆቴል የመሰብሰቢያ አዳራሽ እንደሚያደርጉ በደብዳቤ ለቦርዱ አስታውቀዋል። ከላይ የሰፈሩት ሁለቱ አካሎች በተለያየ ቦታዎች ጉባኤ እንደሚያካሂዱ ማሳወቃቸውን አግባብነት የሌለው መሆኑን ገልፃ፣ ምርጫ ቦርድ በሁለቱም ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ታዛቢ ሳይልክ ቀርቷል። ዝግጅት ክፍላችን ከላይ የሰፈረው ውዝግብ እንደተጠበቀ ሆኖ፣ አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ በጠራው አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ ላይ በመገኘት ያጠናከረውን ዘገባ እና በእነአየለ ስሜ ጠቅላላ ጉባኤ የተመረጡትን ፕሬዝደነት ቃለ ምልልስ ይዞ ቀርቧል። ዘገባው […]