እሳት በዳጋ እስጢፋኖስ
በዳጋ እስጢፋኖስ ገዳም ተነሥቶ የነበረው እሳት በደቅ ደሴት ሕዝብ፣ በገዳማውያኑና በፖሊስ ትብብር መጥፋቱ ተነገረ፡፡ እሳቱ ቁጥቋጦዎችን ከማጥፋት በቀር ደኑን እንዳላወደመው ተነግሯል፡፤ የደቅ ደሴት ሕዝብ ላደረገው አስቸኳይ ርብርብ ገዳማውያኑ ምስጋና አቅርበዋል፡፡ የክልሉ መንግሥትም ሄሊኮፕተር ለመላክ እስከመዘጋጀት ድረስ ያሳየውን ትብብር ገዳማውያኑና ሕዝቡ አድንቀዋል፡፡