ተስፋ ቢሱ የደቡብ ሱዳን ድርድር

ከአዲስ አበባ እስከ ታንዛኒያዋ አሩሻ ከተማ በዘለቀው የደቡብ ሱዳን የአንድ ዓመት የድርድር ሂደት የተኩስ አቁም ለማድረግ እና የሽግግር መንግስት ለመመስረት የተደረጉ ስምምነቶች ተግባራዊ መሆን አልቻሉም። በምስራቅ አፍሪቃ የልማት በይነ መንግሥታት ባለ ስልጣን- ኢጋድ የሚመራው ድርድር በዚህ ሳምንት መጨረሻ እንደገና ይጀመራል ተብሎ ይጠበቃል።