የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መሰደድና «ሲ ፒ ጄይ»

ባለፉት ዓመታት ከኢትዮጵያ የሚሰደደዉ ጋዜጠኛ ቁጥር በእጥፍ መጨመሩን የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ድርጅት «CPJ» ገለፀ። እንደ ድርጅቱ ዘገባ፤ የኢትዮጵያ መንግሥት የጀመረዉን የእስራት ዘመቻ በመፍራት ባለፉት 12 ወራቶች ብቻ ከኢትዮጵያ ከሰላሳ በላይ ጋዜጠኞች ተሰደዋል።