የዓመቱ የዓለም ኮከብ አትሌት ተሰየመ

ዓለማቀፉ የአትሌትክስ ፊደሪሽኖች ማኅበር «IAAF» የዓመቱን የዓለም ኮከብ አትሌቶች ምርጫ ትናንት ምሽት ሞናኮ ላይ ባካሄደዉ ልዩ የሽልማት ሥነ-ስርዓት ላይ ይፋ አድርጎአል። ኢትዮጵያዊትዋ አትሌት ገንዘቤ ዲባባ በዉድድሩ ለእጩነት ቀርባ የነበረ ቢሆንም የኮከብነቱን መዕረግ ሳታገኝ ቀርታለች።