የአውሮጳ ህብረት፣ ዩክሬይን እና ሩስያ

የአውሮጳ ህብረት ውጭ ጉዳይ ሚንስትሮች በምሥራቅ ዩክሬይን ዓማፅያን አንፃር አዲስ ማዕቀብ ለመጣል ተስማሙ። የህብረቱ ዲፕሎማቲክ ክፍል በዚህ በተያዘው የህዳር ወር መጨረሻ ውሳኔ የሚሰጥበት አንድ የዩክሬይንን ዓማፅያን ዒላማ ያደረገ አዲስ ዝርዝር እንዲያቀርብ የውጭ ጉዳይ ሚንስትሮቹ ጠይቀዋል።