9ኙ ፓርቲዎች የጠሩት የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባ በኃይል ተበተነ
ዛሬ ህዳር 7/2007 ዓ.ም 9ኙ ፓርቲዎች በትብብር የጠሩት የአደባባይ ህዝባዊ ስብሰባ በፖሊስና በደህንነት ኃይሎች ተበትኗል፡፡ ፓርቲዎቹ ለሰላማዊ ሰልፍና ስብሰባ ማሳወቂያ ክፍል ያሳወቁ ሲሆን የፓርቲዎቹ አመራሮች ለፖሊስና ደህንነቶች ቢያሳዩም ‹‹የምናውቀው ነገር የለም፣ እኛ ታዘን ነው፡፡ ከፈለጋችሁ አለቆቻችን ሂዳችሁ አናግሩ፡፡›› በማለት ለስብሰባው የተዘጋጁትን ቁሳቁሶች ስብሰባው ሊደረግበት ከታሰበው ሜዳ እንዲነሱ አድርገዋል፡፡
የፓርቲዎቹ አመራሮችና በስብሰባው ለመሳተፍ ወደቦታው ያቀኑ አካላት ለማሳመን ጥረት ቢያደርጉም ፖሊስ ግን ህዝቡን በኃይል በትኗል፡፡