የስደተኞች ጎርፍ በዮርዳኖስ

ባለፉት ዓመታት ዮርዳኖስ ከአካባቢዉ ሃገራት ወደ ሃገርዋ የሚገቡትን በርካታ ስደተኞች ስትቀበል ቆይታለች። ወደ ዮርዳኖስ የሚገቡት ስደተኞች በመጀመርያ ከፍልስጤም ከዝያ ከኢራቅ ነበር አሁን ደግሞ ከሶርያ በርካታ ስደተኞች በመፍለስ ላይ ናቸዉ። ይህች በንጉሳዊ አስተዳደር የምትመራ ትንሽ ሀገር የስደተኛ ጉዳይ ከባድ ፈተና ሆኖባታል።