ኢጋድ ደቡብ ሱዳንን አስጠነቀቀ

የደቡብ ሱዳን ተፋላሚ ኃይላት ከድርጊታቸው ካልተቆጠቡ የምሥራቅ አፍሪቃ የልማት በይነ-መንግስታት ባለሥልጣን በምህጻሩ ኢጋድ እንደሚቀጣቸው በድጋሚ አስጠነቀቀ። አስፈላጊ ከሆነም ኢጋድ ደቡብ ሱዳን ውስጥ ጣልቃ ሊገባ እንደሚችል ዝቷል። የደቡብ ሱዳን አማፂያን በበኩላቸው የደቡብ ሱዳን መንግስት ስምምነቱን ጥሶ ውጊያ ከፍቶብናል ሲሉ ከሰዋል።