የገንዘብ ርዳታ ለአፍሪቃ ቀንድ ሀገራት

የአውሮጳ ህብረት፣ የዓለም ባንክ እና ሌሎች ያካባባ የልማት ባንኮች ለአፍሪቃ ቀንድ ሀገራት ስምንት ቢልዮን ዶላር ርዳታ ለመስጠት ቃል ገቡ። ይህ ዜና ይፋ የሆነው የተመድ ዋና ጸሐፊ ፓን ኪ ሙን ከዓለም ባንክ ፕሬዚደንት ጂም ዮንግ ኪም ጋር ዛሬ ኢትዮጵያን በጎበኙበት ጊዜ ነው።