የኢትዮጵያዊቷን ሬስቶራንት በእንግሊዝ አረጋውያን ተወዳጅ ያደረገው ምንድን ነው?

በኢትዮጵያ አረጋውያን ከቤተሰባቸው ጋር እስከ መጨረሻው ሞኖራቸውን አውሮፓውያኑም ሊወርሱት የሚገባ ባህል ነው የምትለው ቱቱ መላኩ በእንግሊዟ ሬዲንግ ከተማ ፓልመር ፓርክ አካባቢ ካፌና ሬስቶራንት አላት። አብዛኞቹ ደንበኞቿ የዕድሜ ባለፀጋዎች ናቸው። አንድ ሳምንት ከምግብ ቤቷ ከጠፉ አያስችላትም። ስልኳን አንስታ ጤንነታቸውን ትጠይቃለች።