አንጌላ ሜርክል በጀርመን የውኅደት ቀን ምስጋና አቀረቡ
መራሒተ-መንግስት አንጌላ ሜርክል በጀርመን 25ኛ የውኅደት ቀን ዛሬ ሐኖቨር ከተማ ለተሰበሰቡ በሺህዎች ለሚቆጠሩ ታዳሚያን ንግግር አደረጉ። መራሒተ-መንግሥቷ ጀርመንን በምሥራቅ እና ምዕራብ ጎራ ከፍሎ የነበረው የበርሊን ግንብ የዛሬ 25 ዓመት እንዲደረመስ አስተዋፅኦ ያደረጉ የምስራቅ ጀርመን ሰልፈኞችን ጀግንነት እና ጥረት በንግግራቸው አወድሰዋል።