የስኮትላንድ ውሳኔ ሕዝብ

በሰሜናዊው ጫፍ የብሪታንያ ግዛት አካል ስኮትላንድ ፤ እጎአ በ2012 በተደረገ ስምምነት መሠረት፣ ተገንጥላ የራሷን ነጻነት ለማወጅ ወይም ከ 300 ዓመት በላይ ጸንቶ በቆየው ሕብረት፣ ዩናይትድ ኪንግደም በሚባለው ሀገር፣ ማለትም በብሪታንያ በሕብረት ለመኖር፤ ከሁለቱ አንዱን ለመምረጥ፣ ህዝቡ ከዛሬ ጧት አንስቶ እስከማታ ድምፁን በመስጠት ላይ ነው።