ኢትዮ-ቻናል እና የፊት ገጹ

ኢትዮ-ቻናልሲቆላመጥቻናልይባላል፡፡ በአገር ቤት በሳምንት ሁለት ጊዜ ለመታተም የታደለ ጋዜጣ ነው፡፡ ባለፈው ሳምንት የረቡዕ ዕትሙ “የዲያስፖራ ፖለቲካን” ክፉኛ የሚተቹ ጽሑፎችን እንጂ አንድም የተለመደ የጋዜጣ ዜና ይዞ አልወጣም፡፡ በፊት ገጹ የመጀመርያ ርእሰ-ጉዳይ ያደረገው “ኢትዮጵያን ሪቪው” የተሰኘውን ተነባቢ ድረ-ገጽን ነው፡፡ የድረ-ገጽን ባለቤት አቶ ኤልያስ ክፍሌ ከኤርትራው ፕሬዝዳንት ኢሳያሳ አፈወርቂ ጋራ የተነሱትን ባለቀለም ፎቶ አትሞታል፡፡ የሚከተለውን ርዕስ ሰጥቶታል-“ጽንፈኛ ዲያስፖራዎች በሰሜን አሜሪካ እግር ኳስ ላይ የዘቀጠ ፖለቲካቸውን ይዘው ገቡ፡፡ የኢሳያስ ቅጥረኛ የኾነው ኢትዮጵያን ሪቪው ሰርጎ ገብቷል፡፡”

ከዚህ ዜና ባሻገር ብርቱካንን፣ ዶ/ር ያዕቆብን እና መኢአድን የሚተቹ የተለያዩ ገጾቹን የሸፈኑ ጽሑፎች ነበሩት፡፡ የቻናል ገጾች ትችት ብቻ አይደለም የያዙት፤ ሙገሳም አለበት፡፡ ለምሳሌ በፊት ገጹ “ማለቂያ የሌለው ደግነት” በሚል ርእስ ቢሊየነሩን ሼሕ አል-አሙዲንን የሚያሞካሽ ረዥም ጽሑፍ ከእነፎቶግራፋቸው አትሟል…  [ይቀጥላል]