ጀርመን የኢራቅ ኩርዶችን ለማስታጠቅ መወሰኗ

የጀርመን መንግሥት የኢራቅ ኩርዶችን ለማስታጠቅ መወሰኑ የሰሞኑ የጀርመናውያን አብይ የመነጋገሪያ ርዕስ ነው ። የጀርመን መንግሥት ባለሥልጣናት እስከ ዛሬ ሳምንት ሐሙስ ድረስ የሚሰጧቸው መግለጫዎች ጀርመን ጦርነት ወደ ተባባሰባት ኢራቅ የጦር መሣሪያዎችን አትልክም የሚል ነበር ።