ያልሰከነዉ የእስራኤልና ሃማስ ጦርነት

በእስራኤልና ሃማስ ታጣቂ ኃይሎች መካከል የተኩስ አቁም ዉል ድርድር ከተቋረጠ ወዲህ ሁለቱ ወገኖች ተመልሰዉ አንዱ ሌላዉ ላይ ጥቃት መሠንዘር ቀጥለዋል። ዘገባዎች እንደሚሉት እስራኤል ዛሬ ባጠናከረችዉ የጦር አዉሮፕላን ድብደባ ጋዛ ዉስጥ ሁለት ትላልቅ ሕንፃዎችን መትታለች።