ማብቂያ ያጣው የቦኮ ሀራም ሽብር እና ናይጄሪያ

የኤቦላ ወረርሽኝ የመነጋገሪያ ርዕስ በሆነባት ናይጄሪያ ፤ ከበሽታው ሌላ ህዝቧን ያሳሰበው ሌላም ነገር አለ። ይህም በሀገሪቱ ስር የሰደደው አማፂው እስላማዊ ቡድን ቦኮ ሀራም ነው። አማፂያኑ በተቆጣጠሩት ሰሜን ናይጄሪያ እስላማዊ ካሊፋት መመሥረታቸውን በገለፁበት በአሁኑ ወቅት በሌላ በኩል ታግተው የተወሰዱትን ሴት ተማሪዎች ለማስመለስ ትግል ተይዟል።