የጀርመን የስለላ ቅሌት

የጀርመን ፊደራል የስለላ መሥሪያ ቤት ቱርክን ሲሰልል ቆይቷል የቀድሞዋንና የአሁኑን የአሜሪካን ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ስልኮች ጠልፏል መባሉ ማነጋገሩን ቀጥሏል ። የጀርመን ፖለቲከኞች እስካሁን በጉዳዩ ላይ ምንም ያልተናገረው የሐገሪቱ መንግስት ማብራሪያ እንዲሰጥ ግፊት እያደረጉ ነው ።