ወያኔ ቆርጦ መቀጠልም ተሳናት !
ሳምሶን አስፋው – አውስትራሊያ
የአቶ አንዳርጋቸው ቃልና የወያኔ ፕሮፓጋንዳ
ሰሞኑን በወያኔ መንግስት የፖሊስ ፕሮግራም የቀረበው “አቶ አንዳርጋቸው ለመንግስት ጠቃሚ መረጃ ሰጡ” የሚለው ዜና ኢትዮጵያዊውን ሁሉ እያነጋገረ ያለ ጉዳይ ነው። የዜናው አነጋጋሪነት የሚነሳው ለዜናው አብይ ግብአት እንዲሆን፤ በወጉም ሳይታሰብበት ተለጣጥፎ የቀረበው የቪዲዮ ክሊፕ የዜናውን ጩኸት አለማስተጋባቱ ነው። በመጀመሪያ የምናነሳው ጥያቄ የወያኔ ባለስልጣናት ይህንን በተራ ግለሰብ እንኳ ቢቀርብ የሚያሳፍር ደካማ የማስመሰል ስራ በመንግስት ደረጃ ለማቅረብ ያስገደዳቸው ምንድነው? የሚለውን ጥያቄ ይመስለኛል። ለዚህ ደግሞ የተለያዩ መላምቶችን መሰንዘር እንችላለን።