የጋዛው ድብደባ ተጠናክሮ መቀጠል

የእስራኤል የጋዛ ድብደባ ዛሬም ተጠናክሮ ቀጥሏል ። እስራኤል ተጨማሪ ተጠባባቂ ጦር ወደ ጋዛ አዝምታለች ። የፍልስጤም ደፈጣ ተዋጊዎችም ወደ ደቡባዊ እስራኤል ሮኬቶችን መተኮሳቸውን ቀጥለዋል ። ስደተኞች በተጠለሉበት በጋዛው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ትምሕርት ቤት ላይ የደረሰውን ጥቃት የተባበሩት መንግሥታት ድርጅትና አሜሪካን አውግዘዋል ።