በእስራኤል ፍልስጥኤም ግጭት የኃያላኑ አቋም

ሁለት ሣምንታትን ያስቆጠረው የእስራኤል ፍልስጥኤም ግጭት አሁንም ድረስ አልተቋረጠም። በፍልስጥኤም በኩል ከ600 በላይ፣ ከእስራኤል ወገን ደግሞ ወደ 30 የሚጠጉ አይሁዶች መገደላቸው ተዘግቧል። የአረብ ሊግ እና የአውሮፓ ኅብረትን ጨምሮ የተመድ ብሎም ዩናይትድ ስቴትስ ግጭቱን ለማስቆም ከፍተኛ ጥረት በማድረግ ላይ መሆናቸው ተጠቅሷል።