ጀርመን ዋንጫውን ወሰደች

የጀርመን ብሔራዊ እግር ኳስ ቡድን ከእርጀቲና ቡድን ጋር ባደረገው የዋንጫ ግጥሚያ አርጀንቲናን አንድ ለባዶ በመርታት የዋንጫ ባለቤት ሆነ። እስከ በመደበኛው የጨዋታ ጊዜ ፍፃሜ ሁለቱ ቡድኖች ባዶ ለባዶ ስለነበሩ ጨዋታው መራዘም ግድ ነበረበት። ከዚያም በ113 ኛ ደቂቃ ማርዮ ገትስ ባስቆጠራት ግብ ነበር ጀርመናውያን ድል ሊቀዳጁ የቻሉት።