ታጣቂ ቡድኖች በማዕከላይ አፍሪቃ ሬፓብሊክ የደቀኑት ስጋት
በማዕከላይ አፍሪቃ ሬፓብሊክ የብረቱ ትግል ከተጀመረ ከአንድ ዓመት ተኩል ገደማ በኋላም በብዙው የሀገሪቱ አካባቢ በቀድሞ ሙሥሊሞች የሴሌካ ዓማፅያን እና በአንፃራቸው በሚንቀሳቀሱት የፀረ ባላካ ሚሊሺያዎች መካከል ግጭቱ አሁንም እንደቀጠለ ነው። ሀገሪቱም ከግጭት አዙሪት መውጣት ተስኗታል። መንግሥትም ቀውሱን የማስቆም አቅም ተጓድሎት ይገኛል።