ኢትዮጵያዊያን በቶሮንቶ መለስን ተቃውመው ለመሰለፍ እየተሰናዱ ነው

ከዋሽንግተን ዲሲና ከቫንኩቨር ድረስ ኢትዮጵያዊያን እየገቡ ነው

ተክለሚካኤል አበበ-ከቶሮንቶ

እንደ ፈረንጆቹ አቆጣጠርኸ ከጁን 26 እስከ ጁን 27 በሚካሄደው የጂ 20 ስብሰባ ላይ ለመሳተፍ ይመጣል ተብሎ የሚጠበቀውን አቶ መለስ ዜናዊና ተከታዮቹን ለመቃወም ከፍተኛ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑንና ከሰሜን አሜሪካ የተለያዩ ከተሞች አያሌ ኢትዮጵያዊያን ወደ ቶሮንቶ ይገባሉ ብለው እንደሚጠብቁ አዘጋጆቹ ገለጹ።