ሁለት ወራት በማዕከላዊ


በትላንትናው ዕለት የዞን ዘጠኝ አባላት እና ጋዜጠኞች ከታሰሩ 60ኛ ቀናቸውን (ሁለተኛ ወራቸውን) አስቆጥረዋል እስካሁን ማስረጃ ያልቀረበባቸውና በሕገ-መንግስቱ ሊከበርላቸው የሚገቡ መብቶች ሁሉ ተንደው በማዕከላዊ የምርመራ ጣቢያ እተሰቃዩ ይገኛሉ የዞን ዘጠኝ አባላት እና ጋዜጠኛ ጓደኞቻቸው በምንም አይነት ሕገ-ወጥ ተግባር ላይ ያልተሳተፉ ሕገ-ወጥነትን የሚጠየፉና መንግስት ሕገ-መንግስቱን አክብሮ እንዲሰራ የሚወተውቱ ሃላፊነት የሚሰማቸው ዜጎች ናቸው፡፡

Poster Credit Mahilet Solomon

ያለአግባብ የታሰሩት ጓደኞቻችን ያለቅድመ ሁኔታ እንዲፈቱ ዛሬም ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡
#FreeZone9Bloggers #FreeEdom #FreeAsmamaw #Ethiopia