በሺዎች የሚቆጠሩ ስደተኞች ኢጣሊያ ገቡ

የኢጣሊያ ባህር ኃይል ዳግም በሺ የሚቆጠሩ የጀልባ ላይ ስደተኞችን ማዳኑን አስታወቀ። እንደ ባህር ኃይሉ ከሆነ በጥቂት ሰዓታት ውስጥ ከ3000 በላይ ስደተኞችን ከኢጣሊያ የባህር ጠረፍ ተቀብሏል። ከሰሜን አፍሪቃ በኩል እንደመጡ የተነገረዉ አብዛኞቹ ስደተኞች ወደ ሲሲሊያ መወሰዳቸውም ተነግሯል።