የተስፋይቱ ምድር የኢትዮጵያ ልጆች ሆይ!
መስፍን ማሞ (ሲድኒ-አውስትራሊያ)
ለቀደሙት የተባለውን ሰምታችዃል……… ይህም ተፅፏልና!
ለምትበልጠው ፀጋ ቅኑ። እኔም ዳግመኛ እጅግ የበለጠ ሌላ ጎዳና አሳያችዃለሁ፤ በሰዎች ሁሉ ቋንቋና በመላእክት ቋንቋ ብናገር፤ ትንቢትም ብናገር፤ የተሰወረውን ሁሉና የጥበብን ሥራ ሁሉ ባውቅ፤ ተራራም እስካፈልስ ድረስ ሃይማኖት ቢኖረኝ፤ ያለኝንም ሁሉ ለድሆች ባበላ፤ ዳግመኛም ሥጋዬን ለእሳት ቃጠሎ ብሰጥ፤ ፍቅር ከሌለኝ የተጠቀምሁት የለም። ፍቅር ያለው ሰው ሩህሩህ ትዕግስተኛም ነውና።