የአዉሮጳ ኅብረት የምክር ቤት ቅድመ ምርጫ ዉጤት

ጀርመንን ጨምሮ በአውሮጳ ኅብረት 21 አባል ሃገራት ውስጥ ዛሬ ከጠዋት ጀምሮ የተደረገዉ የምክር ቤት ምርጫ ቅድመ-ዉጤት መዘርዝር መዉጣት ጀምሮአል። መጀመሪያ ላይ ይፋ በሆነው ቅድመ-ዉጤት መዘርዝር መሰረት ወግ አጥባቂዎቹ የክርስቲያን ዲሞክራቲክ ኅብረትና የክርስትያን ሶሻል ኅብረት ፓርቲ « CDU/CSU» በ36.1 በመቶ እየመራ መሆኑ ተገልጿል።