የአውሮጳ ቡድኖች የዋንጫ ፍልሚያዎች

ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በተለያዩ የሩጫ ውድድሮች ድል ተቀዳጅተዋል። አትሌቲኮ ማድሪድ ከ18 ዓመታት በኋላ የስፔን ላሊጋ አሸናፊ ሆኗል። የጀርመኑ ባየር ሙንሽን ተቀናቃኙ ቦሩስያ ዶርትሙንድን ድል ነስቶ ዋንጫውን በእጁ አስገብቷል። የጣሊያን ሴሪኣ ዋንጫን ጁቬንቱስ ጨብጧል። የእንግሊዝ «FA-Cup» ዋንጫን መድፈኞቹ ለንደን ይዘው ገብተዋል።