ቦኮ ሃራም ላይ ያነጣጠረዉ የፓሪሱ ጉባኤ

ፈረንሳይ ፓሪስ ላይ የተደረገዉ ፀረ- ሽብር ጉባኤ፤በተለይ በናይጀርያ በሚንቀሳቀሰዉ አሸባሪ ደፈጣ ተዋጊ ቡድን ቦኮ ሃራም ላይ ማነጣጠሩ ተመለከተ። የናይጀርያዉን አሸባሪ ቡድን ለመዉጋት፤ በተሻለና በተቀናጀ መንገድ የትብብር ሥራ ወሳኝ መሆኑም ዛሬ ፓሪስ ላይ በተካሄደዉ የደኅንነት ጉባኤ ላይ ተመልክቶአል።