የጉዞ ማስጠንቀቂያና የኬንያ ቱሪዝም

ናይሮቢ ኬንያ ዉስጥ ዛሬ በደረሰ ፍንዳታ ቢያንስ አስር ሰዉ ሳይገደል እንዳልቀረ ተገለጸ። በርካቶችም ተጎድተዋል። የኬንያ ብሄራዊ የአደጋ መከላከል ዘመቻ ማዕከል ፍንዳታዉ የደረሰዉ በህዝብ ማመላለሻ መለስተኛ አዉቶቡስና ገበያ ዉስጥ መሆኑን ገልጿል። ለፍንዳታዉ እስካሁን ኃላፊነት የወሰደ አካል የለም።