የቦኮሃራም ጥያቄና የታገቱት ልጃገረዶች

የናይጀሪያው የሙስሊም ፅንፈኛ ቡድን ቦኮ ሃራም ከትምህርት ቤት ያገታቸውን ልጃገረዶች ለመልቀቅ ያስቀመጠውን ቅድመ ሁኔታ የናይጀሪያ መንግሥት እንደማይቀበል አስታወቀ ። ቡድኑ ልጃገረዶቹን ለመልቀቅ የታሰሩበት ሚሊሽያዎች እንዲለቀቁ ያቀረበውን ጥያቄ የናይጀሪያ መንግሥት ውድቅ አድርጎታል ።