ደ.ሱዳን፤ የተኩስ አቁም ስምምነት ተፈረመ

በደቡብ ሱዳን ለወራቶች ከዘለቀ ከፍተኛ ግጭትና ጦርነት በኋላ፤ የደቡብ ሱዳኑ ፕሬዚዳንት ሳል ቫኪርና ተቀናቃኛቸዉ የቀድሞዉ ጠቅላይ ሚኒስትር ሪኤክ ማቸር የተኩስ አቁም ስምምነት ተፈራረሙ። ይህ ትናንት ምሽት የተደረሰዉ ስምምነት፤ በተፈረመ በ24 ሰዓታት ዉስጥ ተግባራዊ እንደሚሆን ተገልፆአል።