የጆን ኬሪ የአፍሪቃ ጉብኝት

የዩናይትድ ስቴትስ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጆን ኬሪ ዛሬ ማምሻውን አዲስ አበባ ይገባሉ ተብሎ እየተጠበቀ ነው ። የስድስት ቀናት የአፍሪቃ ጉብኝታቸውን በኢትዮጵያ የሚጀምሩት የኬሪ ትኩረት የሰብአዊ መብቶች ቀውስ በተከሠተባቸው አካባቢዎች የሚሰጥ እርዳታ እንዲሁም የኤኮኖሚ ትብብር እንደሚሆን ተገልጿል ።