የተባባሰው የደቡብ ሱዳን ግጭት

የደቡብ ሱዳን ግጭት እስካሁን በሺህዎች የሚቆጠሩ የሀገሪቱ ነዋሪዎችንለሞት ዳርጓል። ከአንድ ሚሊዮን በላይ ሰዎችም ቀዬያቸውን ጥለው እንዲሰደዱ አስገድዷል። ከወራት በፊት በሁለቱ የደቡብ ሱዳን ተፋላሚ ኃይላት መካከል አዲስ አበባ ውስጥ የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተፋላሚዎችን ደም ከመፋሰስ አልታደገም።