ሰልፍና ሰደፍ፤

ልጅ ተክሌ (ቶሮንቶ)

ዘመቻ ነቀምትና ዘመቻ ኢትዮጵያ

፩-      የሲያትሉ ባተሌ ወዳጄ ደውሎ፤ “አንድነት የአዲስ አበባውን ሰልፍ ፈቃድ ተከልክሏል፡፡ ስለዚህ ምን ርምጃ ይውሰድ” በሚል ጥያቄ ሲያደርቀኝ ነበር፡፡ ሳንግባባ ተለያየን፡፡ ከሞላ ጎደል እሱ የሚለው፤ “ቢከለከሉም ገፍተው ይውጡ፡፡ ምክንያቱም፤ በተከለከሉ ቁጥር እሺ ብለው የሚገቡ ከሆነ፤ በህዝብ ዘንድ ተቀባይነት ያጣሉ፡፡ ገፍተው ከወጡ ግን፤ መንግስትም ጨክኖ ርምጃ አይወስድም፤ ቢወስድም ግን፤ ትግሉን ያበረታል፤ ሌሎችንን ይቀሰቅሳሉ” ነው፡፡ ኢፍትሀዊ ህግን መጋፈጥ ፍትሀዊነት ነው የሚለውን ይትበሀል ይዞ መሰለኝ የሞገተኝ፡፡ እኔ ደግሞ “የለም ሁሉንም ሰብስቦ ያስራቸዋል፤ ካሰራቸው ደግሞ ሌሎች ሰልፈኞች መውለድ አመታት ይፈጃል፡፡ ስለዚህ ይታገሱ፤ ሲሆን ሲሆን ወደፍርድቤት ይሂዱ፤ ወይም ሌላ ጥበብ ፈጥረው ሂደቱን ያጡዙት፡፡ እንጂ፤ አሁን ገፍተው ሰልፍ ቢወጡ ትግሉን ማጨናገፍ፤ ማስወረድ ነው” ብዬ ሞገትኩ፡፡ አልተስማማንም፡፡  የዚህ ጽሁፍ አብይ ዓላማም ማስታወቂያና ማስታወሻ ቢሆንም፤ የኛ የወጤዎቹ (ዳያስፖራ) ሚና የት ድረስ ነው? ድርጅቶቻችንስ ከመፈክር የዘለለ አመራር ለመስጠት ምን ሸበባቸው? በማለት፤ ከቅዳሜ ኤፕሪል 26ቱ የቶሮንቶ-ነቀምት ዝግጅት ማስታወሻ ጎን ለጎን፤ ሌሎች ጉዳዮችን በስሱ ያሻሻል፡፡ ከዚያ በፊት ግን፤

ሙሉውን አስነብበኝ …