የሊቢያ ህገ መንግሥት አርቃቂ ኮሚቴና ተግባሩ

ህገ መንግሥቱን የሚያረቁት ተወካዮች በሃገሪቱ ስር እየሰደደ የሄደውን ፖለቲካዊና ጎሳዊ ግጭቶች በተለይ በምስራቅ የሃገሪቱ ክፍል የሚቀርበውን የተጠናከረ የራስ ገዝ አስተዳደር ጥያቄ ግምት ውስጥ ማስገባት እንደሚኖርባቸው ተመልክቷል ። ረቂቁ እንደተጠናቀቀ ለህዝበ ውሳኔ ይቀርባል ተብሎ ይጠበቃል ።