አሳሳቢው የደቡብ ሱዳን ውጊያ

በደቡብ ሱዳን ታጣቂዎች በቦር፣ ጆንግሌይ የሚገኘውን የተመድ ሰፈር አጥቅተው ቢያንስ 50 ሰዎች ገደሉ። በዚሁ ቢያንስ 5000 ሰዎች ከለላ ባገኙበት ሰፈር በተጣለው ጥቃት ከቆሰሉት መካከልም ሁለት የተመድ ሰላም አስከባሪዎች ይገኙባቸዋል።