በካይ ጋዞችን ለመቀነስ የግለሰብ ጥረት

የአየር ንብረትን አስመልክቶ በተመድ የተካሄደ አንድ ጥናት ታዳሽ የኃይል ምንጭን መጠቀም አማራጭ እንደሌለዉ አመለከተ። በርሊን ላይ ይፋ የሆነዉ ይህ ጥናት በርካታ ካርቦን ዳይኦክሳይድ ከተከማቸበት ከቅሪተ አፅም ከሚገኘዉ የኃይል ምንጭ ዓለም ባስቸኳይ ተላቆ ከባቢ አየርን ከጉዳት እንዲያድን ይማጸናል።