ሚሊዮኖች ድምጽ – የአንድነት ብሄራዊ ስራ አስፈፃሚዎች የነገውን የአዲስ አበባ ቅስቀሳ ይመሩታል፡፡

አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) የእሪታ ቀን በሚል መሪ ቃል በአዲስ አበባ የጠራው ሰላማዊ ሰልፍ በተያዘለት ቀንና ቦታ እንደሚካሄድ ለመገናኛ ብዙሀን ካሳወቀበት ከትላንትናው እለት ማለትም መጋቢት 24/2006 ዓ.ም ጀምሮ ለከተማዋ ነዋሪዎች ስለሰልፉ ዓላማ የሚገልፅ በራሪ ወረቀት እያሰራጨ ይገኛል፡፡እስካሁን ድረስ ከ10.000 ሺ በላይ በራሪ ወረቀቶች ተሰራጭተዋል ፡፡ የነገውን ቅስቀሳ የአንድነት ብሔራዊ ስራ አስፈፃሚ እና የአዲስ አበባ ከተማ የአንድነት ስራ አስፈፃሚ እንዲሁም የሁለቱ ምክር ቤት አባላት ይመሩታል ተብሎ ይጠበቃል፡፡